addisnews

I'm standing for real freedom. I regard freedom of expression as the primary right without which one can not have a proper functioning democracy.

Archive for the day “August 18, 2013”

አሳዛኝ ዜና ! ድምፃዊ ኢዮብ መኰንን አረፈ !!!

111
ድምፃዊ ኢዮብ መኰንን ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ ባደረበት ድንገተኛ ሕመም ራሱን ስቶ በሕክምና ላይ እንደሚገኝ ታወቀ፡፡ በአስጊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የተገለጸው ኢዮብ የሕመሙ መንስዔ ስትሮክ መሆኑ ታውቋል፡፡

የቅርብ ጓደኞቹ ድምፃዊው ይህ ነው የሚባል ሕመም እንዳልነበረበትና ታሞ እንደማያውቅ ገልጸው፣ ባለፈው እሑድ ድንገት እጁ ላይ በተሰማው ስሜት ምክንያት ሐያት ሆስፒታል ለመታየት ቢሄድም ሙሉ ጤነኛ እንደነበር ተነግሮታል፡፡

ባለፈው ማክሰኞ ብስክሌት እየነዳ ልጁን ከትምህርት ቤት አስመዝግቦ ሲመለስ ቤቱ በር ላይ ተዝለፍልፎ በመውደቁ፣ ቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል ድንገተኛ ክፍል ገብቶ እስካሁን ድረስ ራሱን ስቶ እንደሚገኝ ተረጋግጧል፡፡

ወደ ኬንያ ሄዶ እንዲታከም ለማድረግ የኢዮብ ወዳጆች ኮሚቴ አዋቅረው ገንዘብ አሰባስበውለታል፡፡ በአገር ውስጥ የአውሮፕላን አምቡላንስ ባለመኖሩ ምክንያትም በኬንያ ከሚገኝ የግል ኩባንያ ጋር በ25,000 ዶላር ወስዶ ለማሳከም ስምምነት ላይ መደረሱ ታውቋል፡፡

ለሕክምናው የሚያስፈልገው ወጪ ከጓደኞቹና ከጥበብ ማኅበረሰቡ እየተሰባሰበ ሲሆን፣ ባለፈው ዓርብ ሐኪሞቹ እስከሚፈርሙ ድረስ እየተጠበቀ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በከተማው ውስጥ አሉ የሚባሉ ኒውሮሎጂስቶችና ሌሎች የሕክምና ባለሙያዎችም እየመረመሩት ነበር፡፡

በማሽን እየተረዳ የሚተነፍሰው ኢዮብ እስካሁን በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ በግልጽ አልታወቀም፡፡ በጭጋጋማና ብርዳማዎቹ ቀናት አድናቂዎቹ፣ ዘመዶቹና ወዳጆቹ ስለጤንነቱ እየጸለዩና እስኪነቃም እየተጠባበቁ መሆናቸው ታውቋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በፌስቡክ ድረ ገጽ ላይ ‹‹ለኢዮብ መኮንን እንጸልይ›› የሚል ገጽ የተፈጠረለት በመሆኑ፣ በርካቶች መልካም ምኞታቸውንና ጸሎታቸውን ለድምፃዊው እያስተላለፉ ነው፡፡

ታዋቂው ሙዚቀኛ ኢዮብ ሬጌን በተለየ መልኩ በመዝፈን የራሱን አሻራ ማሳረፍ የቻለ ነው፡፡ ‹‹እንደቃል›› በሚለው አልበሙ ተወዳጅነትና ተደማጭነትም ማግኘት ችሏል፡፡ በመድረክ አያያዙና በመሳጭ ግጥሞቹ የብዙዎችን ልብ ማሸነፍ እንደቻለም ይነገርለታል፡፡

ጅጅጋ ከተማ ውስጥ የተወለደው የ37 ዓመቱ ኢዮብ፣ የሙዚቃው ተፅዕኖ ከዝነኛው ድምፃዊ አሊ ቢራና ከቦብ ማርሌ እንዳረፈበት መናገሩ ይታወሳል፡፡

አሁን በደረሰን ዜና ኢዮብ መኰንን በ ማረፉን ሰምተናል ለቤተሰቡ መፅናናትን እንመኛለን

ለአቡነ ጳውሎስ የመቃብር የነሐስ ሐውልት የተመደበው 1.5 ሚልዮን ብር ነው

55
የአቡነ ጳውሎስ ሙት ዓመት ትናንት ታስቦ ውሏል። ይህን ተከትሎ በወጡ መረጃዎች የሟቹን ፓትርያርክ የመቃብር ሐውልት በነሐስ ለማሠራት 1.5 ሚልዮን ብር የተመደበ መሆኑ ታውቋል። የሐራ ሙሉ ዘገባ እንደወረደ ይኸው፦
ለሐውልቱ ሥራ የተዋዋለው ተቋራጭ አድራሻውን አጥፍቶ ጀርመን ከረመ
በውሉ መሠረት ከነሐስ የሚሠራውን ሐውልት በ186 ቀን ሠርቶ ማስረከብ ነበረበት
ለጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ‹‹ዝክረ አበው›› እንዲያደርስ ታዝዟል

ነሐሴ ፲ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም ሌሊት ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ የተለዩት የአምስተኛው ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ኅልፈት አንደኛ ዓመት መታሰቢያ ሥነ ሥርዐት በዛሬው ዕለት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በማሕሌት፣ በጸሎተ ፍትሐትና በቅዳሴ ታስቦ ውሏል፡፡

በቤተ ክርስቲያናችን የሙታን መታሰቢያ ቀኖና መሠረት በዐጸደ ነፍስ ያሉትን ዕጣን፣ ጧፍ እና መሥዋዕት በማቅረብ ተዝካረ ጸሎት ማድረግ ሥርዐት መኾኑን ከመጽሐፈ ግንዘት እና መጽሐፈ ሢራክ በመጥቀስ ያስረዱት ብፁዕ አቡነ ገሪማ፣ የአቡነ ጳውሎስ ዕረፍት አንደኛ ዓመት መታሰቢያ የሚካሄደው ‹‹ቅዱስነታቸው በሁሉም አቅጣጫ ያስመዘገቧቸውን የሥራ ውጤቶች በማዘከር›› መኾኑን ገልጸዋል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከዐሥራ አንድ ያህል ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋራ የሙት ዓመት መታሰቢያ ሥነ ሥርዐቱን መርተዋል፤ ንግግራቸውም ‹‹ነፍሰ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያሪክ አባ ጳውሎስን ከማኅበረ መላእክት፣ ከማኅበረ ጻድቃን እንድትደምርልን እንለምንሃለን›› በሚል የተወሰነና የተጠቃለለ ነበር፡፡

ጸሎተ ፍትሐቱ በተከናወነበት የካቴድራሉ ዐጸድ ውስጥ የሚገኘውና ሥራው ያልተጠናቀቀው መካነ መቃብራቸው በእብነ በረድ ተዘግቷል፤ በቆርቆሮ የታጠረው ዐጸድ ዙሪያው ጒንጒን አበባ ተደርጎበት የቀድሞውን ፓትርያሪክ ግዙፍ ምስል በያዘ ባነር ተሸፍኗል፤ ‹‹መልካሙን ገድል ተጋድያለኹ. . .›› የሚለው የቅዱስ ጳውሎስ ጥቅስ በታላላቅ ፊደላት ሰፍሮበታል፡፡ የመታሰቢያ ሥነ ሥርዐቱ ተካፋዮች ከጸሎተ ፍትሐቱ በኋላ ወደተቀጸረው የመካነ መቃብሩ ዐጸድ ቢዘልቁም ከዚህ በቀር የሚያዩት ነገር አልነበረም፡፡

የመቃብር ሐውልቱ ሥራ ስለመዘግየቱ የተመለከቱ ጥያቄዎችና ቅሬታዎች ለመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ መድረሳቸውን የገለጹት የጽ/ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፣ ሐውልቱ ከነሐስ እንዲሠራ ተወስኖ ሥራውን ለማስፈጸም የተቋቋመው ኮሚቴ ለክንውኑ በተመደበው ገንዘብ መሠረት ጨረታ አውጥቶ ለአሸናፊው ተቋራጭ ውል ተሰጥቶ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

‹‹በጨረታው ውል መሠረት ተቋራጩ ሥራውን በ186 ቀን ጨርሶ ማስረከብ ነበረበት፤ ባለማጠናቀቁ ለመንፈቅ እንዲያደርስ ተራዘመለት፤ አላደረሰም›› ያሉት ብፁዕነታቸው፣ ‹‹ስልኩንም አጥፍቶ ነሐሴ 6 ቀን ብቅ ብሎ ጀርመን ነበርኹ ብሎ አረዳን›› ሲሉ እርሱ እየተጠበቀ ሥራው ከውሉ ውጭ እስከ ሙት ዓመት ድረስ መዘግየቱን አስረድተዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ለሐውልቱ ሥራ የተመደበው ገንዘብ [1.5 ሚልዮን ብር መኾኑ ተዘግቧል] በባንክ ተጠብቆ እንዳለ መኾኑን ገልጠው÷ ‹‹እብነ በረዱ ተስተካክሎ ተቀምጧል፤ ተቋራጩም ነሐሱን [ከነሐስ የተሠራ ምስላቸውን] አምጥቼ ማቆም ብቻ ነው የሚቀረው ብሎናል፤ በተገባው ውል መሠረት ለጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ባሉበት ይመረቃል፤ የዘገየው በእኛ ምክንያት አይደለም፤ ይህን እንድትረዱልን ነው፤›› ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

በቀድሞው ዘመነ ፕትርክና ይኹን አሁን የፓትርያሪኩ ልዩ ጽ/ቤት ሓላፊ የኾኑት ብፁዕ አቡነ ገሪማ በንባብ ባሰሙት ዝክረ ፓትርያሪክ አቡነ ጳውሎስ፣ ‹‹በዘመናቸው 49 ኤጲስ ቆጶሳትን አስገኝተዋል›› ብለዋል፡፡ ለአንደኛ ዓመት መታሰቢያ በብፁዕነታቸው ተዘጋጅቶ በሥነ ሥርዐቱ ላይ የተሠራጨውና የፓትርያሪኩን ዜና ሕይወትና ሥራዎች የያዘው ኅትመትም የአቡነ ጳውሎስን ኅልፈት አስመልክቶ የሚከተለውን አስፍሯል፤

ይኹንና ‹‹መኑ ሰብእ ዘየሐዩ ወኢይሬእያ ለሞት፤ ሕያው ሁኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ሰው ማን ነው?›› /መዝ.88÷48/ ተብሎ በነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በተነገረው መሠረት ቅዱስ ፓትርያርካችን በጾመ ፍልሰታ ለማርያም በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤተ ክርስቲያን በመቀደስና ሐዋርያዊ ተልእኮ በመፈጸም አንደኛውን ሱባኤ ካጠናቀቁ በኋላ ነሐሴ 8 ቀን 2004 ዓ.ም በዐሥራ አንድ ሰዓት አካባቢ ለምርመራ ወደ ሆስፒታል ሄደው በመታከም ላይ እንዳሉ ነሐሴ 10 ቀን 2004 ዓ.ም ከንጋቱ 11፡00 በተወለዱ በ76 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል፡፡

ለረጅም ጊዜ የአቡነ ጳውሎስ መጋቤ ሥርዐት ኾነው ያገለገሉት ፕሮቶኮል ሹማቸው ሙሉጌታ በቀለ ስለ ጤንነት ይዞታቸውና ድንገተኛ ኅልፈታቸው ነሐሴ ፲፪ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም በፓትርያሪኩ የቀብር ሥነ ሥርዐት አፈጻጸም ሂደት ላይ ተወያይቶ መርሐ ግብር ለማውጣት ተሰብስቦ በነበረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ፊት ቀርበው እንደሰጡት የተነገረው የቃል አስረጅ ደግሞ ፓትርያሪኩ ከተባለው ሰዓት ቀደም ብለው ስለማረፋቸው የሚጠቁም ነው፤

ማክሰኞ [ነሐሴ 8 ቀን] በቅድስት ማርያም አስቀድሰው ነበር፤ ከቅዳሴ ከወጡ በኋላ ከተወሰኑ አባቶችና እንግዶች ጋራ ምሳ በሉ፤ እኔም ወደ ቤቴ ሄድኩ፤ ማምሻውን አመማቸው ተባለና ተጠርቼ መጣኹ፤ ጤንነታቸውን በግል የሚከታተለው ዶ/ር ተጠርቶ መጣና አያቸው፤ ለክፉ የሚሰጥ አይደለም ብሎ ሄደ፤ ነገር ግን ሕመም ስለጠናባቸው ብዙ ጊዜ ወደሚታከሙበት ባልቻ ሆስፒታል ይዣቸው ሄድኹ፤ ሐኪሞቹ ሲመረምሯቸው ሳምባቸው ውኃ ቋጥሯል፤ ፈቃድዎ ከኾነ ውኃውን እንቅዳው ብለዋቸው ኦፕሬሽን ክፍል ገብተው ተቀዱ፤ ረቡዕ ተሽሏቸው ሰውም ሲያናግሩ ውለው ነበር፤ እኩለ ሌሊት ገደማ ግን ተጫጫነኝ ሲሉኝ ተረኛ ዶክተሮችን ጠርቼ አዩዋቸው፤ ዕረፍት እንዲያደርጉ አዘዟቸው፤ እኔም ከጎን ወደነበረ ማረፊያ ክፍል ሄድኩ፤ ንጋት ላይ ወደ ክፍላቸው ስመለስ ዐርፈው አገኘኋቸው፡፡

በወቅቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የአማርኛ ቋንቋ አገልግሎት ሲናገሩ፣ ‹‹አብረን አስቀድሰን ቢሮም አብረን ቆይተን ነበር፤ ፓትርያሪኩ በስኳር ሕመም ይታወቁ ነበር፤ ጾሙም ሕመማቸውን ሳያከፋው አልቀረም፤ ብቻ ታመው አቅኑኝ ሳይሉ ፃዕር ጋዕር ሳይበዛባቸው ቅዳሴውን ሳያቋርጡ ከቤተ ክርስቲያን ወደ ቤተ ክርስቲያን ነው የሄዱት፤›› ብለው ነበር፡፡

ሌሎች ምንጮች በበኩላቸው የፓትርያሪኩን ሕመም ያከፋው÷ በወቅቱ ይፋ ያልተደረገውን የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኅልፈት ሲረዱ በደረሰባቸው ከፍተኛ ድንጋጤና ይህን ተከትሎ ይወስዷቸው የነበሩትን መድኃኒቶች አወሳሰድ ማስተጓጎላቸው ያስከተለባቸው ‘multiple organ failure’ እንደነበረ ሲናገሩ ቆይተዋል፡፡

የፓትርያሪክ አቡነ ጳውሎስ ቤተ ዘመዶች ‹‹የአቡነ ጳውሎስ ፋውንዴሽን›› ለማቋቋም መንቀሳቀስ መጀመራቸው ከመንበረ ፓትርያሪኩ ምንጮች ተሰምቷል፡፡ ይህ ፋውንዴሽን በፓትርያሪኩ ፳ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በሼራተን አዲስ በተከበረበት ወቅት ራእይ ለትውልድ የተሰኘው አካል በስማቸው ‹‹የካንሰር፣ቲቢና ኤድስ የሕክምናና ማገገሚያ ማእከል›› በ200 ሚልዮን ብር ለመገንባት ካቀደበት የበዓለ ሢመት ስጦታ ጋራ ግንኙነት ይኖረው እንደኾነ አልታወቀም፡፡

የፓትርያሪኩ ኅልፈት በተሰማበት ዕለት ረፋድ መኖርያ ቤታቸው፣ በስጦታ ያገኟቸው አይከኖች፣ መስቀሎች፣ አልባሳትና ሽልማቶች የሚገኙበት ሙዝየም ፖሊስና የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጠቅላላ አገልግሎት በተገኘበት መታሸጉ ተገልጦ የነበረ ቢኾንም ከአሮጌ አልጋና ካገለገሉ አልባሳት በቀር የተገኘ ነገር አለመኖሩ ተጠቁሟል፤ በምትኩ ፓትርያሪኩ በሽልማት ያገኟቸው አራት መኪኖች የይገባናል ጥያቄ እንደቀረበባቸውና ለዚህም ክሥ እንደሚመሠረት ተሰምቷል፡፡

ቢያንስ ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦት ፳፻፭ ዓ.ም የርክበ ካህናት ምልአተ ጉባኤው በቀድሞው ፓትርያሪክ ንብረት ላይ ለመወሰን የያዘው አጀንዳም በቂ ውይይት እንዳልተካሄደበትና ውሳኔም እንዳልተሰጠበት ነው ለመረዳት የተቻለው፡፡ በ፲፱፻፺፩ ዓ.ም ሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ ፵፭ ንኡስ አንቀጽ (፩) እና (፪) ‹‹ስለ ቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ሀብትና ንብረት›› ግን የሚከተለው ተደንግጓል፤

አንድ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ከዚህ ዓለም በሞት በሚለይበት ጊዜ የግል የኾነ ገንዘብ ቢኖረው ይረዳቸው ለነበሩ ዕጓለሙታንና ችግረኞች ይሰጣል፡፡ (አብጥሊስ ፴፱)
ኤጲስ ቆጶሱ መንፈሳዊ አገልግሎቱን ሲያከናውንባቸው የቆዩ መጻሕፍት፣ አልባሳት፣ አርዌ ብርት፣ መስቀሎች፣ መቋሚያዎችና የመሳሰሉት ሁሉ በቤተ ክርስቲያኒቱ ንብረትነት በስሙ ተመዝግበው በሀገረ ስብከቱ በሙዝየም ይቀመጣሉ፡፡
ነገር ግን እንደ ሕጉ አልኾነም፤ እንዲኾንም ተከታትሎ የሚጠይቅና የሚያስፈጽም አካል ያለ አይመስልም፡፡ እንዲያውም የታዛቢዎች አስተያየት የሚያስረዳው የቀድሞው ፓትርያሪክ ዜና ኅልፈት ከተሰማበት ዕለትና ከዚያም በኋላ የአንዳንድ ጉዳዮች አያያዝ፣ ‹‹ሲደከምበትና በብርቱ ሲፈለግ የቆየው የአቡነ ጳውሎስ ኅልፈት ብቻ እንደነበረና ሁሉም ነገር ከኅልፈታቸው ጋራ አብሮ ያከተመ የሚያስመስል ነው፡፡››

Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/

አላቋርጥ ያለው አምባገነንት፣ አልከስት ያለው ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ (ኢሕአፓ)

44ላለፉት አርባ ዓመታት በአገራችን እየተካሄደ ያለውን የለውጥ እንቅስቃሴ ገድል ስናስብ፣ እንቅስቃሴው የተጓዘበትን እያንዳንዱን ምዕራፍ በራሱና ለብቻው እንዳለ ማየታችን ተቀዳሚና ዋና ቢሆንም፣ ከሌሎች ምዕራፎች ጋር የሚያያዝበትን ብዙ ገመድ፣ የሚለያይበትን ባህርይና የሚመሳሰልበትን ጎን መርምረን በጎና ጎጂ ገጽታዎቹን በነቂስ ማጤኑ ለቀጣዩ የትግል ምዕራፍ ሂደት አስፈላጊ መሆኑ አይካድም። ይህን ማድረጉ፣ ቀጣዩ የትግል ምዕራፍ ለሂደቱ ካለፈው በጎውን ወስዶ ጎጂውን ደግሞ ዳግም እንዳይከሰትና እንቅስቃሴውን እንዳያጓትት የሚረዱ ዝግጅቶችን ሁሉ የማድረግን አስፈላጊነት የሚያስተምር ይሆናል። ከዚያም በላይ እንቅስቃሴው አላማዬና ግቤ ብሎ ካነገበው ዋና ቁም ነገር ስኬታማ ከመሆኑና ካለመሆኑ ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በቅጡ የተያያዘ መሆኑንም ጭምር ያጤንበታል።

Read more: http://www.ethiolion.com/Pdf/08162013Democracia-Hamle-2005.pdf

ጁነዲን ሳዶ ተገደሉ የሚለው ዜና ሃሰት ነው ተባለ

33
(ዘ-ሐበሻ) ፌስቡክን ጨምሮ በተለያዩ የማህበራዊ ድረገጾች ላይ በሰፊው እየተወራ የሚገኘው የአቶ ጁነዲን ሳዶ በወያኔ ተገደሉ የሚለው ዜና ሃሰት መሆኑን ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ሰዎች እየገለጹ ነው። እነዚህ ለአቶ ጁነዲን ቅርብ ነን ያሉ ወገኖች “የወሬው ምንጭ ሁሌም ሕዝብን በወሬ ማራበሽ የሚወደው የወያኔ መንግስት ነው” ይላሉ።
ወጣቱ የፖለቲካ ተንታኝ ጃዋር መሀመድ በፌስቡክ ገጹ “ጁነዲን ተገደሉ የሚለው ዜና ሃሰት ነው” ሲል በተለይ በአያንቱ ድረገጽ ላይ የወጣውን ዜና አስተባብሏል። አያንቱ ድረ ገጽ Gurmessaa Beekamaa የተባሉ ሰው በፌስቡክ የለጠፉትን ዜና “ይህ ዜና ከነፃ ምንጮች አልተረጋገጠም” በሚል በማቅረብ ዜናው እንዲቀጣጠል ያደረገ ቢሆንም፤ ድረገጹ ከሰዓታት በኋላ ደግሞ ጁነዲን በሕይወት ስለመኖራቸውና ስላለመኖራቸው የተምታታ መረጃዎች እየደረሰን ነው በሚል ጉዳዩን እያጣራ እንደሚገኝና የዜናው ምንጭ ናቸው የተባሉት ግለሰብም ስለጁነዲን ተጨባጭ ማስረጃቸውን እንዲያቀርቡ ጠይቋል።
የወያኔ ሚዲያ እንደሆነ የሚነገርለት ኢትዮቻናል የተባለውና በሃገር ቤት የሚታተመው ጋዜጣ ከዚህ ቀደም ጁነዲን ሳዶ ወደ ኬንያ ጠፍተዋል በሚል ሃሰተኛ ዜና ማሰራጨቱ የሚዘነጋ አይደለም ያሉት እነዚሁ የጁነዲንን ሞት የሚያስተባብሉ ወገኖች አሁንም ተገደሉ ብሎ የሚያወራው ራሱ ወያኔ፤ የሕዝቡን የአስተሳሰብ አቅጣጫ ለመቀየር ነው ይላሉ። በተለይ በነፃው ፕሬስ ላይ ለረዥም ዓመታት የሰሩ አንድ አንጋፋ ጋዜጠኛ ለዘ-ሐበሻ እንደገለጹት “የወያኔ መንግስት ሃሰተኛ ዜናዎችን በመፈብረክ ሚዲያዎች ተአማኒነት እንዲያጡ ለማድረግ ሲጥር ይህ የመጀመሪያው አይደለም። በነፃ ጋዜጦች ስም የራሱን ጋዜጦች በማሳተም ሃሰተኛ ዜናዎችን እያቀረበ በራሱ ቴሌቭዥን ደግሞ ‘ነፃ ጋዜጠኛ የሚባሉት እንዲህ እያሉ የውሸት ዜና እየጻፉ ነው’ የሚል ፕሮፓጋንዳ በመሥራት ራሱ በከፈተው ነፃ ጋዜጣ ሌላውን ነፃ ጋዜጣ ሲያሰደብና ተአማኒነት እንዲያጡ በማድረግ ቆይቷል። አሁን ደግሞ እንዲህ ያለው ዜና፣ ባለፈው ዓመት መንግስቱ ኃይለማርያም በዙምባብዌ ሞቱ የሚሉት ዜናዎች በራሱ በወያኔ ተዘጋጅቶ በፌስቡክ የሚለጠፈው ፌስቡክ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ለውጥ እንደሚያመጡ ስለሚያውቅ መንግስት ሕዝቡ ፌስቡክ ላይ የሚጻፉ መረጃዎችን እንዳያምን ለማድረግ ነው የተዘጋጀ ድራማ ነው” ይላሉ።
የጁነዲን ሳዶ ባለቤት በወያኔ መንግስት ሽብርተኛ ተብለው የታሰሩ ሲሆን ይህን ተከትሎም ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርነታቸው መነሳታቸው ይታወሳል። ጁነዲን የሕወሓት ተለጣፊ ከሆነው ኦሕዴድ ጋር በሚሰሩበት ወቅት በአውስትራሊያ እና በሚኒሶታ ከፍተኛ ተቃውሞ አጋጥሟቸው እንደነበር መዘገቡ ይታወሳል።

Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=642

በድምፃዊ ኢዮብ መኰንን ላይ የተፈጠረው ድንገተኛ ሕመም አድናቂዎቹን አስደንግጧል

22
ድምፃዊ ኢዮብ መኰንን ካለፈው ማክሰኞ ጀምሮ ባደረበት ድንገተኛ ሕመም ራሱን ስቶ በሕክምና ላይ እንደሚገኝ ታወቀ፡፡ በአስጊ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ የተገለጸው ኢዮብ የሕመሙ መንስዔ ስትሮክ መሆኑ ታውቋል፡፡

የቅርብ ጓደኞቹ ድምፃዊው ይህ ነው የሚባል ሕመም እንዳልነበረበትና ታሞ እንደማያውቅ ገልጸው፣ ባለፈው እሑድ ድንገት እጁ ላይ በተሰማው ስሜት ምክንያት ሐያት ሆስፒታል ለመታየት ቢሄድም ሙሉ ጤነኛ እንደነበር ተነግሮታል፡፡

ባለፈው ማክሰኞ ብስክሌት እየነዳ ልጁን ከትምህርት ቤት አስመዝግቦ ሲመለስ ቤቱ በር ላይ ተዝለፍልፎ በመውደቁ፣ ቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል ድንገተኛ ክፍል ገብቶ እስካሁን ድረስ ራሱን ስቶ እንደሚገኝ ተረጋግጧል፡፡

ወደ ኬንያ ሄዶ እንዲታከም ለማድረግ የኢዮብ ወዳጆች ኮሚቴ አዋቅረው ገንዘብ አሰባስበውለታል፡፡ በአገር ውስጥ የአውሮፕላን አምቡላንስ ባለመኖሩ ምክንያትም በኬንያ ከሚገኝ የግል ኩባንያ ጋር በ25,000 ዶላር ወስዶ ለማሳከም ስምምነት ላይ መደረሱ ታውቋል፡፡

ለሕክምናው የሚያስፈልገው ወጪ ከጓደኞቹና ከጥበብ ማኅበረሰቡ እየተሰባሰበ ሲሆን፣ ባለፈው ዓርብ ሐኪሞቹ እስከሚፈርሙ ድረስ እየተጠበቀ መሆኑ ተገልጿል፡፡ በከተማው ውስጥ አሉ የሚባሉ ኒውሮሎጂስቶችና ሌሎች የሕክምና ባለሙያዎችም እየመረመሩት ነበር፡፡

በማሽን እየተረዳ የሚተነፍሰው ኢዮብ እስካሁን በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ በግልጽ አልታወቀም፡፡ በጭጋጋማና ብርዳማዎቹ ቀናት አድናቂዎቹ፣ ዘመዶቹና ወዳጆቹ ስለጤንነቱ እየጸለዩና እስኪነቃም እየተጠባበቁ መሆናቸው ታውቋል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በፌስቡክ ድረ ገጽ ላይ ‹‹ለኢዮብ መኮንን እንጸልይ›› የሚል ገጽ የተፈጠረለት በመሆኑ፣ በርካቶች መልካም ምኞታቸውንና ጸሎታቸውን ለድምፃዊው እያስተላለፉ ነው፡፡

ታዋቂው ሙዚቀኛ ኢዮብ ሬጌን በተለየ መልኩ በመዝፈን የራሱን አሻራ ማሳረፍ የቻለ ነው፡፡ ‹‹እንደቃል›› በሚለው አልበሙ ተወዳጅነትና ተደማጭነትም ማግኘት ችሏል፡፡ በመድረክ አያያዙና በመሳጭ ግጥሞቹ የብዙዎችን ልብ ማሸነፍ እንደቻለም ይነገርለታል፡፡

ጅጅጋ ከተማ ውስጥ የተወለደው የ37 ዓመቱ ኢዮብ፣ የሙዚቃው ተፅዕኖ ከዝነኛው ድምፃዊ አሊ ቢራና ከቦብ ማርሌ እንዳረፈበት መናገሩ ይታወሳል፡፡

ethiopian reporter

የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ችግሮች ና አንድምታው

dd
በኢትዮጵያ የሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች አያያዝ አሁንም ማነጋገሩ ቀጥሏል ። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በኢትዮጵያ የሙስሊሞች የሐይማኖታዊ ነፃነት ጥያቄ ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን በዚያው መጠን መንግሥት የሚወስደው እርምጃ እየጠነከረ ሄዷል ።
ዓለም ዓቀፍ የመብት ተሟጋች ድርጅቶች የውጭ መንግሥታትና የሐገር ውስጥ ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሃገሪቱ ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንደማይከበሩ በየአጋጣሚው ማሳወቃቸው አልቆመም ። የኢትዮጵያ መንግሥት ግን ይህን አይቀበልም ። ከዚያ ይልቅ በህገ መንግሥቱ የሰፈሩትን እነዚህን መብቶች በማክበር ላይ መሆኑን ነው የሚገልፀው ። ሆኖም ተቃዋሚ ፖለቲከኞችና የመብት ተሟጋቾች በፀረ ሽብርና በፕሬስ ህጉ ሰበብ ጋዜጠኞችና ፖለቲከኞችን መታሰራቸውን የመብት ጥያቄ ያነሱ ሙስሊሞችም ለሞት ለእስርና ለእንግልት መዳረጋቸው መቀጠሉን ይናገራሉ ። በቅርቡ የአደባባይ ሰልፍና ህዝባዊ ስብሰባዎች ያደራጁ ና ያካሄዱ የሐገር ውስጥ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አባላቶቻቸው እስርና ወከባ እንደተፈፀመባቸው አስታውቀዋል ። ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በኢትዮጵያ የሙስሊሞች የሐይማኖታዊ ነፃነት ጥያቄ ተባብሶ የቀጠለ ሲሆን በዚያው መጠን መንግሥት ጥያቄውን በሚያቀርቡ ወገኖች ላይ የሚወስደውም እርምጃ እየጠናከረና እየከፋ መጥቷል ። በተቃዋሚዎች ላይ ጠንክሯል ። ይህ እንዴት ይታያል ? ወዴትስ ያመራል ? በዚህ ጉዳይ ላይ እንዲወያዩልን 3 እንግዶችን ጋብዘናል ። አቶ ግርማ ሰይፉ በኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል ፣ አምባሳደር ጥሩነህ ዜና የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ኮሚሽነር ፣ እና አቶ ያሬድ በአሁኑ ሰዓት በስደት ላይ የሚገኙ የቀድሞ የሰብዓዊ መብት ጉባኤ አባል ናቸው ።
ሂሩት መለሰ
ልደት አበበ
AUDIOS AND VIDEOS ON THE TOPIC

የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝ ችግሮች
http://www.dw.de/popups/mediaplayer/contentId_17026241_mediaId_17026242
http://www.dw.de

መንግስት የሼህ ኑሩ ይማምን ግድያና የሙስሊሙን ተቃውሞ ከአንድነት ፓርቲና ኢሳት ጋር ሊያያዝ ሞከረ

11
ነሃሴ ፲(አስር)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :- መንግስት ትናንት ሼህ ኑሩን ማን ገደላቸው በሚል ርእስ በኢቲቪ በለቀቀው ዘጋቢ ፊልም ላይ አንድነት ፓርቲ የሼህ ኑሩን ግድያ ደግፎ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲጠራ ማድረጉን የግንቦት7 ልሳን የሆነው ኢሳት ቴሌቪዥንም አሸባሪዎችን ” አይዞአችሁ በርቱ” እያለ ድጋፍ እንደሰጣቸው አንድ ግለሰብን በማናገር አቅርቧል

በዘጋቢ ፊልሙ ላይ ሶስት ተጠርጣሪ ገዳዮች ቀርበው የሚናገሩ ሲሆን፣ ፊልሙ ከአንዱ ክፍል ተቆርጦ ከሌላው ክፍል እየተገጣጠመ የተቀናበረና ገዳይ የተባሉትም ከፉኛ የተደበደቡ በሚመስል መልኩ ለመናገር ሲቸገሩ ይታያል።

አንድነት ፓርቲ ”የሙስሊሞችን ጥያቄና የሼክ ኑሩን ግድያ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ማያያዝ ወንጀል ነው” በሚል ርዕስ ባወጣው መግለጫ ዘጋቢ ፊልሙ መቅረቡን በጽኑ ተቃውሞአል።

ፓርቲው ፊልሙ ” የገዥውን ፓርቲ ብፅእና ከመተረክም በላይ ጉልበተኝነትንና ፍረጃን ማእከል አድርጎ ከአኬልዳማ እና ከጃሀዳዊ ሀረካት የቀጠለ በፓርቲያችን እና በዜጎች ላይ የተቃጣ ህገ ወጥ የፕሮፓጋንዳ ስራ ነው” ብሎታል፡፡

የመንግስትነት ስልጣን የያዘ አካል ሀገራዊ ችግሮችን ለምን በዶክመንተሪ ፊልም ለመፍታትና ለማዳፈን እንደሚጥር እንቆቅልሽ ሆኖብናል የሚለው አንድነት ” የሙስሊም ጥያቄ በውይይትና በመግባባት ላይ ተመስርቶ ሊመለስ እንደሚገባና የሀይል እርምጃው መቆም እንዳለበት አሳስቧል።

ፊልሙ የኢህአዴግ የፍረጃ ፖለቲካ የተንፀባረቀበት፤ የተለየ ሀሳብና ጥያቄ ያቀረቡ ግለሰቦችንና ተቋማትን ማሸማቀቅ ብሎም የማጥፋት እኩይ ተግባር ማሳያ መሆኑንም ፓርቲው ገልጿል። አንድነት ፍርድ ቤት በተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ አድርጎ ውሳኔ ሳያሳልፍ በቴሌቪዥን ፍርድ መስጠቱ ገዢው ፓርቲ በህግ የማይገዛ አምባገነን ስለመሆኑ ግልጽ ማሳያ ሲሆን የፍትህ ስርዓቱ ልዕልናም በአንድ ቴሌቪዥን ጣቢያ መገፈፉን ገልጿል።

የኢትዮጵያ ሬድዮ እና ቴሌቪዥን ድርጅት የፓርቲያችን አመራሮች በየግዜው የሚያደርጉትን ንግግሮች ሞያንና ንጹህ ህሊናን በሚያጎድፍ መልኩ እየቆራረጠ ሙሉ ትርጉሙን እንዳይዝ አድርጎ በማስተላለፍ እየፈጸመ ያለው አሳፋሪ ተግባር እንዲታረም፣ በሼህ ኑሩ ላይ የተፈጸመው ግድያ በየትኛውም አካል የተፈጸመ ቢሆንም ህገ ወጥ እና ኢሰባአዊ መሆኑን ፓርቲው ጠቅሷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ መንግስት በክርስቲያኑና በሙስሊሙ መካከል ልዩነት እንዲፈጠር እየሰራ ነው በማለት አንዳንድ የህብረተሰብ ክፍሎች ለኢሳት ገልጸዋል።

መንግስት በተለያዩ ቀበሌዎች ስብሰባዎችን እየጠራ ክርስቲያኑ ወገን በሙስሊሙ ጥያቄ ፍርሀት እንዲሰማው እያደረገ መሆኑን እነዚሁ አስተያየት ሰጪዎች ገልጸዋል።

መንግስት በአሁኑ ሰአት በመላ አገሪቱ የሀይማኖት ጉበኤ መክፈቱ ታውቋል።

Post Navigation