addisnews

I'm standing for real freedom. I regard freedom of expression as the primary right without which one can not have a proper functioning democracy.

Archive for the day “October 17, 2013”

አንድ ከሰዓት በመንበረ ፓትርያርክ

የመንበረ ፓትርያርክ 32ኛው ጉባኤ የረቡዕ ዕለት ከሰዓት ውሎ ካለፉት የተለየ ነበር፡፡ ዋና አጀንዳው ‹መቻቻልን› የተመለከተ ሲሆን አቅራቢዎቹም ከፌዴራል ጉዳዮች የተወከሉ አካላት መሆናቸውን በዕለቱ የመርሐ ግብር ዝርዝር ላይ ተገልጧል፡፡ ከሰኞ ጀምሮ ይቀርብ በነበረው የአህጉረ ስብከት ሪፖርቶች ላይ የመብት ጥሰትና ሥልጣንን ለግል ሃይማኖት ማስፋፊያ የመጠቀም አዝማሚያዎች መኖራቸውን፣ በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጠው እምነትን የመያዝ፣ የማስፋፋትና የአምልኮ ቦታ የማግኘት መብት እየተጣሰ መሆኑን የሚገልጡ ዘገባዎች ይሰሙ ነበር፡፡
 
በትናንትናው የከሰዓት ውሎ ስለ መቻቻል ገለጣ ከተሰጠ በኋላ ብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳትና የጉባኤው ተሰብሳቢዎች የየአካባቢያቸውን ችግሮች በዝርዝር ነበር ያነሷቸው፡፡ ‹‹መቻቻል እስከ ምን ድረስ ነው›› ብለው ነበር ብጹዕ አቡነ ቄርሎስ የጠየቁት፡፡ ‹‹አሁን በምዕራብ ወለጋ ያለው ሁኔታ መንግሥት በአገሩ ያለ ይመስላል ወይ? ሰው እግሩን እሳት እየበላው ቻል ይባላል እንዴ? እንድንቻቻል አድርጉን፣ እንችላለን›› ነበር ያሉት፡፡
የምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ሄኖክ ‹በነጆ ወረዳ በሕጋዊ መንገድ ተሠርቶ የነበረው ቤተ ክርስቲያን በአካባቢው ባለ ሥልጣናት ተጽዕኖ እንዲፈርስ መደረጉን፣ ለምን ታፈርሳላችሁ ብለው ድርጊቱን የተቃወሙ ስድሳ ምእመናን መታሠራቸውን›› በኀዘን ነበር የገለጡት፡፡ አያይዘውም ‹‹በባኮ ወረዳ የተመደቡ አንድ ካህን እያረሱ እያሉ የአካባቢው ባለ ሥልጣናት መጡ፤ ካህኑን በሰደፍ እየደበደቡ ‹ከዚህ ሀገር ልቀቁ፣ ይህ የነፍጠኛ መኖሪያ አይደለም› እያሉ አሰቃዩዋቸው፡፡ ካህኑን ሲደበድቧቸው አንበርክከው፣ ለ15 ደቂቃ አተኩረው ፀሐይዋን እንዲያዩ እያስገደዱ ነበር፡፡ ድብደባውን ሰምተው የወጡት ባለቤታቸው በድንጋጤ ታመው ከጥቂት ቀናት በኋላ ሕይወታቸው አለፈ››
‹‹በሰንበትና በቅዱስ ሚካኤል ቀን ምእመናን ሊያስቀድሱ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲሄዱ ‹ለቅዳሴ ካህናቱ ይበቃሉ፤ እናንተ ውጡ›› እየተባሉ እንዳያስቀድሱ ይደረጋሉ፡፡ ከእኛ ቤተ ክርስቲያን 70 ሜትር ርቀት ላይ ሆን ተብሎ እርስ በርስ ለማጋጨት ለፕሮቴስታንቶች የጸሎት ቦታ ተሰጠ፡፡ ለምን ታጨቃጭቁናላችሁ፤ ይህ ቦታ ለእነርሱ አይሆንም ብሎ በመከራከሩ አንድ ዲያቆን ተደብድቦ ሞተ፡፡ የሕክምና ውጤቱም ሆን ተብሎ በወባ በሽታ ሞተ ተብሎ ተሠራ፡፡ ለሁለት ዓመት ያህል ተከራክረን አሁን ቦታው ለእኛ ተወሰነ፡፡
ጊምቢና መንዲ ላይ የምእመናን ልጆች ትምህርት ቤት ውስጥ በፖሊስ ማተባችሁን በጥሱ እየተባሉ ነው፡፡ ለምን ስንላቸው ከላይ የወረደ መመሪያ አለ ይሉናል፡፡››
ቀጥለው የሀገረ ስብከታቸውን ችግር ያቀረቡት የጋሞጎፋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኤልያስ ነበሩ፡፡ ‹‹በጋሞ ጎፋ መቱ ወረዳ፣ ዋጁ ኡቆ ላይ የመስቀል ማክበሪያ ቦታችን ለሱቅ መሥሪያ ቦታ ተሰጠ፡፡ አቤት ብንል የሚሰማን በማጣታችን ዘንድሮ በኢትዮጵያ ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ መስቀል ሳናከብር ዋልን፡፡ ሀገሪቱ በችግር ላይ በነበረች ጊዜ እንኳን መስቀል ሳይከበር ቀርቶ አያውቅም ነበር፡፡ የቤተ ክርስቲያን የይዞታ ቦታ ለመንግሥት እየተሰጠ ነው፡፡ በአቡነ ጳውሎስ ዘመን በቅዱስነታቸው በኩል ለክልሉ ደብዳቤ ጻፍን፡፡ ክልሉ ወሰነልን፡፡ ነገር ግን እስካሁን አልተረከብንም፡፡››
ቀጥለው ሃሳባቸውን የሰጡት የባሰ ካልመጣ በቀር ድምጻቸው ማይሰማው ብጹዕ አቡነ ያሬድ የሶማሌ ክልል ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ነበሩ፡፡ ‹‹በሶማሌ ክልል አምስት አብያተ ክርስቲያናት ብቻ ናቸው ያሉን፡፡ ምእመናኑ ብዙ ናቸው፡፡ ሲወልዱ የሚያስጠምቁበት፣ ሲያርፉ የሚቀበሩበት ቤተ ክርስቲያን እንትከል ብንል የሚሰማን አጥተናል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን የሚረዱ ምእመናን በግላቸው ጥቃት እየደረሰባቸው ነው፡፡ ለዚህ መልሳችሁ ምንድን ነው›› ብለዋል፡፡
በገለጻው ላይ ኢትዮጵያ ክርስትናን የተቀበለችው በ4ኛው መክዘ ነው የሚለውን የተቃወሙት ብጹዕ አቡነ ማርቆስ ‹‹ታሪክ ክፉም ሆነ በጎ እንደ ታሪክነቱ መተረክ አለበት፤ አቅራቢው ወንድማችን በ4ኛው መክዘ ክርስትና ገባ ያልከው ተሳስተሃል፡፡ ለመሆኑ ይህንን ለማለት ‹ላይሰንስ አለህ?› አባቱን የሚኮንን ልጅ ምን ያደርጋል? ነገሥታቱን ወቀሳችሁ፣ ቤተ ክርስቲያንን ነቀፋችሁ፤ ለመሆኑ ከማን ነው ይህቺን ሀገር የተረከባችሁት? ክርስትና ወደ ኢትዮጵያ የገባው ጌታ ባረገ ዓመት ባልሞላው ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ በሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ 8 ላይ አለ፡፡ ይህንን ዛሬ ‹ግራጁዌት አድርገው›፤ ልዑካኑ ስትመጡ ስለምትናገሩት ነገር ዕወቁ፤››
የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ እንድርያስም ‹‹በቤተ መንግሥት የወርቅ ዕቃ ብቻ አይኖርም፣ የእንጨትም፣ የድንጋይም ዕቃ አለ፡፡ በቤተ ክርስቲያንም ሁሉም ጥሩ አይሆንም፣ መጥፎም ይኖራል፡፡ ነገር ግን እስከ መጨረሻው የጸና ይድናል ብሏል፡፡ በእኔ ሀገረ ስብከት ስድስት አብያተ ክርስቲያናት ተቃጥለዋል፡፡ ሦስቱ በአንድ አካባቢ፣ ሦስቱ በሌላ ቦታ፡፡ ይህንን ለክልሉ መንግሥት ብናሳውቅ አልረዱንም፡፡ የተበደለ ሰው ይጮኻል፤ ሲጮህ ደግሞ ፖለቲካ ነው ይባላል፡፡ ድሮ ያስቸገረን የንዋያተ ቅድሳት ዘረፋ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ቤተ ክርስቲያን ወደ ማቃጠል ተዛውሯል፡፡ አንዱ ባለ ሥልጣን እንዲያውም ችግሩን ሳቀርብለት ተቆጣኝ፤ ብዙ ብናገር ነፋስ ስለሚወስደው እዚህ ላይ ይብቃ››
ከብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳት ቀጥሎ የተናገሩት የወላይታ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ‹‹በበዴሳ ወረዳ ያለ አንድ የሌላ እመነት ተከታይ የሆነ ዳኛ ከኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጋር ቄራ አንካፈልም፤ በመኪና አብረን አንሄድም› ብሎ ዐወጀ፡፡ በጋራ በመቻቻል የኖርንበትን ዕድር ሁሉ ለዩ ብሏል፡፡ ታድያ እንዴት መቻቻል ሊመጣ ይችላል፡፡››
ከጉባኤው የቀረበውን ቅሬታና ሃሳብ ያዳመጡት የፌዴራል ጉዳዮች የሥራ ኃላፊዎች የቀረቡት ቅሬታዎች በሰነድ ተደግፈው ቢደርሷቸው እነርሱም በመፍትሔው ላይ መሥራት እንደሚችሉ፤ ኢትዮጵያ የሃይማኖቶች ጉባኤም ጉዳዩ በየደረጃው ቢቀርብለት መፍታት እንደሚችል፡፡ ቅሬታዎችን እንደዚህ ባለ መድረክ ከሚሆን በየጊዜው እየተገናኙ መፍታት ቢቻል›. የሚሉ ሃሳቦችን ሠንዝረዋል፡፡
የዘንድሮው የሰበካ አጠቃላይ መንፈሳዊ ጉባኤ በአደረጃጀቱ ውበት፣ በተሳታፊዎቹ ብዛት፣ በአህጉረ ስብከቶች ቁጥር(50 ደርሰዋል)፣ በስብሰባው ቁም ነገረኛነት ካለፉት የተለየ ነበር፡፡ እነ ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ የሰበካ ጉባኤ ስብሰባ ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን በብርቱ እንደ ደከሙበት ያሳያል፡፡ በየዘገባዎቹ የተሰሙትን የመብት ጥሰቶች፣ ሥልጣንን ተገን በማድረግ የሚፈጸሙ ጫናዎች፣ የአምልኮ ቦታ እጥረቶች፣ በካህናቱ ላይ የሚፈጸሙትን ግፎችና፣ የቤተ ክርስቲያንን ይዞታ የመንጠቅ ርምጃዎች ግን ሊገቱ ይገባቸዋል፡፡ ከአንዳንድ ክልሎች በቀር በብዙዎቹ የዞንና የክልል ባለ ሥልጣናት ችግሩን ተረድተው ለመፍታት እንደሚጥሩ ተገልጧል፡፡ በወረዳ ደረጃ የሚገኙት ግን ሥልጣንን ተገን በማድረግ የግል እምነታቸውን እያስፋፉ መሆኑን ያሳያል፡፡ በደቡብ ጎንደርና በምሥራቅ ጎጃም የተፈጸሙት የአብያተ ክርስቲያናትን የማቃጠል ርምጃዎች በጊዜው ተጣርተው መፍትሔ ካልተሰጣቸው ፍጻሜያቸው አያምርም፡፡
በየአካባቢው በሚገኙ ባለ ሥልጣናት የሚፈጸሙ ትንኮሳዎችም መቆም አለባቸው፡፡ ብጹዐን ሊቃነ ጳጳሳቱ ‹አታስቆጡን› እያሉ ደጋግመው የተናገሩት ነገር የዋዛ አይደለም፡፡ ኃላፊነት የማይሰማቸው አካላት የሚፈጽሙት ገደብ አልባ ትንኮሳና ጫና ወዴት እያመራ መሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡
ቤተ ክርስቲያኒቱም አደረጃጀቷንና አሠራርዋን ይበልጥ የምትፈትሽበት፣ አሁን ለገጠማት ተግዳሮት ብቁ የሚሆን አሠራና አወቃቀር የምትይዝበት፣ ችግሮችን በስብሰባ ብቻ ሳይሆን በአካባቢያዊ ውይይት፣ በሕግ መሥመርና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀራርቦ በመሥራት የምትፈታበት መንገድ ሊኖር ይገባል፡፡
ያለበለዚያ መጋቤ ምሥጢር ወልደ ሩፋኤል የተረተው ተረት መድረሱ የማይቀር ነው፡፡
በጣልያን ጊዜ ነው አሉ፡፡ ጎንደር ላይ ጣልያን በድማሚት አንዱን ተራራ ያናውጠዋል፡፡ ተራራው ‹እድም› እያለ ይፈርሳል፡፡ አንዲት የከብት እረኛ ልጅ ፈርታ ወደ እናቷ ሄደችና ‹እማዬ ኧረ ጣልያን ተራራውን እያፈረሰው ነው›› አለቻት፡፡ እናቷም ‹‹እነ ደጃዝማች እገሌ፣ እነ ፊታውራሪ እገሌ፣ እነ ራስ እገሌ እጅ አንሰጥም ብለው እየተጋደሉ ዐለፉ፡፡ ተራራውንስ ተይው ያፍርሰው፤ እርሱም መቀመጡን አብዝቶት ነበረ፡፡›› አለቻት አሉ፡፡
 

ርዕዮትና እስክንድር የኢትዮጵያን መንግስት በአፍሪካ ህብረት ፍርድ ቤት ሊሞግቱት ነው፡፡

Ethiopian Journalists Challenge Anti-Terrorism Law

http://www.globalvoicesonline.org


Ethiopian veteran journalist and blogger Eskinder Nega and journalist Reeyot Alemu have filed a complaint against Ethiopia at the African Commission on Human and Peoples’ Rights, challenging the country’s abuse of its anti-terrorism law to suppress free speech. Both were convicted under Ethiopia’s notorious 2009 Anti-TerrorismProclamation for asking critical questions about government policies — simply put, for doing their job as journalists. Mr. Nega is currently serving an 18-year prison term and Ms. Alemu one of 5 years. Their cases are but two of many more that have been brought under the guise of “combatting terrorism” in the country.
Ethiopia is one of many countries that has adopted anti-terrorism laws modeled after expansive legislation that specifically targets United States policy. Hundreds of journalists and other dissenting voices in the country have been prosecuted under the Anti-Terrorism Proclamation since it entered into force in 2009. With its overly broad provisions, which even explicitly make practising journalism a crime, it has been employed as an effective tool of oppression in a context that wasn’t conducive to a free press to begin with.
Reporters Without Borders ranked Ethiopia 137th out of 179 states in its 2013 World Press Freedom Index, 10 places lower than its 2012 ranking. According to theCommittee to Protect Journalists, more journalists fled into exile from Ethiopia in 2011 than from any other country worldwide and between 2008 and 2013, a total of 45 journalists went into exile from the country. Journalists and opposition political party members face frequent harassment, particularly when their coverage is critical of the government. Self-censorship is a routine consequence of the situation.
Two of the journalists prosecuted under the 2009 Anti-Terrorism Proclamation are Eskinder Nega and Reeyot Alemu. For Mr. Nega, the founder of many independent publications in Ethiopia, all of which have now been shut down, this is the eighth time authorities are persecuting him because of his work. Together with Ms. Alemu, a political columnist for the now-banned independent newspaper Feteh and a regular contributor to the online news outlet Ethiopian Review, he is now challenging the legislation on which he previously wrote critical opinion pieces where he questioned the way the law was being used to jail journalists.
Their petition asks the African Commission to refer the case to the African Court on Human and Peoples’ Rights, which could issue a binding ruling against the Ethiopian government. This is necessary, they argue, because their case is merely an example of the many more journalists, activists and political opponents who are being prosecuted as “terrorists”. Under the African Charter, the Commission has the power to refer matters to the Court that concern a “serious or massive violation” of human rights. The complaint of Mr. Nega and Ms. Alemu sets out that the systematic prosecution of those critical of the government constitutes exactly that.
Their decision to challenge the Ethiopian government is a very brave one. Since their imprisonment, both journalists have suffered repercussions for speaking out on their situation and those of others. Mr Nega and Ms. Alemu have both been denied visitation rights on a frequent basis and Ms. Alemu has been threatened with solitary confinement.
Mr. Nega and Ms. Alemu are represented before the African Commission by Nani Jansen of the Media Legal Defence Initiative, Patrick Griffith of Freedom Now and Korieh Duodu of Lincolns Inn. The next upcoming session of the African Commission will take place in Banjul, The Gambia from 22 October – 5 November 2013.

የአሜሪካን የበጀት ውዝግብና መዘዙ

usa
የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት የሃገሪቱን የበጀት ጣሪያ ከፍ ለማድረግ የሚያስችለውን ስምምነት ትናንት ማታ ካፀደቀ በኋላ ለ16 ቀናት በከፊል ተዘግተው የቆዩት የፌደራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች ዛሬ ሥራ ጀምረዋል ። የትናንቱ ውሳኔ በቅርቡ ስራ ላይ ይውላል ተብሎ የሚጠቀበው አዲሱ የጤና ዋስትና ደንብ መሰረታዊ ለውጥ እንዲደረግበት አጥብቀው ይሟገቱ ለነበሩት ወግ አጥባቂ የሪፐብሊካን ፓርቲ እንደራሴዎች እንደ ሽንፈት ተቆጥሯል ። ሂሩት መለሰ
የዩናይትድ ስቴትስ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት መጀመሪያ 81 የድጋፍና 18 የተቃውሞ ድምፅ ከሰጠበት በኋላ ሪፐብሊካኖች ወደ ሚያመዝኑበት የህግ መምሪያ ምክር ቤት የተመራው ረቂቅ ውሳኔ እሮብ ማታ በ285 ድጋፍና 144 ተቃውሞ ነው ሊያልፍ የቻለው ። የሃገሪቱን የበጀት ጣሪያ ከፍ ለማድረግ ውሳኔ እንዲሰጥበት የተቀመጠው የጊዜ ገደብ እኩለ ለሊት ከመድረሱ አስቀድሞም የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ባራክ ኦባማ በፊርማቸው አፅድቀውታል ። የሃገሪቱ የበጀት ጣሪያ ከፍ እንዳይል ሲሟገቱ የቆዩት ወግ አጥባቂ ሪፐብሊካኖች ውሳኔው እንዲዘገይ ቢያደርጉም ከማለፍ ግን ሊያስቀሩት ባለመቻላቸው ሽንፈታቸውን አምነዋል ።
« ጥሩ ትግል አካሂደናል ። ግን አላሸነፍንም »
ሪፐብሊካኑ የህግ መምሪያ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ጆን ቦህነር ይህን ሲሉ በህግ መወሰኛ ምክር ቤት የብዙሃኑ ዲሞክራቶች መሪ ሃሪ ሬድ ደግሞ የዓለምን ትኩረት የሳበው የዚህ ውዝግብ ድል አድራጊው ዲሞክራሲ ነው ብለዋል ።
obama
ባራክ ኦባማ
« ዛሬ የመንግስት መሥሪያ ቤቶች እንዲከፈቱና የሃገሪቱም የበጀት ቀውስ እንዲስተካከል ለማድረግ በአሜሪካን ምክር ቤት ሁለቱ ፓርቲዎች የደረሱበትን ታሪካዊ ስምምነት ሁሉም ተመልክቷል ።»
ከፖለቲካ ፓርቲ ገለልተኛ የሆነው የበጀት ጉዳዮችን የሚያጠናው መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ኮሚቴ አባልና የምጣኔ ሃብት ምሁር ማርክ ጎልድዌይን ግን ሁለቱም ባሉት አይስማሙም ።
« በዚህ ጉዳይ አሸናፊ የለም በርካታ ተሸናፊዎች ግን አሉ ። እግዚአብሔር ይመሰገን የበጀት ቀውሱን በማስቀረት የመንግሥት መሥሪያ ቤቶች የሚከፈቱበትን መንገድ አግኝተናል ። ይህ በእርግጠኝነት የኤኮኖሚው እድገት እንዲሻሻል ያደርጋል ።»
ትናንት ማታ የፀደቀው ህግ በውዝግቡ ምክንያት ተዘግተው የነበሩ የፌደራል መንግሥት መስሪያ ቤቶች እንደ ጎርጎሮሳውያን አቆጣጠር እስከ ጥር 15 2014 ድረስ ሥራቸውን እንዲቀጥሉ ያስችላል ። መንግሥትም በህጉ መሰረት እስከ የካቲት 7 2014 ድረስ ወይም ከዚያም አንድ ወር ለበለጠ ጊዜ ልትበደር ትችላለች ። ያ ማለት ግን ውዝግቡ ዘላቂ መፍትሄ አገኘ ማለት አይደለም ከዚህ ወሳኝ ግን ጊዜያዊ ውሳኔ በኋላ ተጨማሪ እርምጃዎች መወሰድ ይኖርባቸዋል ። የዲሞክራትና የሪፐብሊካን ፓርቲዎች ተወካዮች የሚገኙበት ኮሚሽን የሃገሪቱን እዳ መቀነስ ያስችላሉ ተብለው በቀረቡ ሃሳቦች ላይ መክሮ በታህሳስ አጋማሽ ውጤቱን ይዞ መቅረብ ይጠበቅበታል ። ጎድዊን እንደሚሉት መፍትሄ ያልተገኘላቸው በርካታ የረዥም ና የአጭር ጊዜ ችግሮች አሉ ።

” src=”http://www.dw.de/image/0,,17150770_404,00.jpg” width=”340″ height=”191″ border=”0″ />

ጆን ቦህነር

« በግብር ከምናገኘው ገቢ በላይ በፍጥነት በመጨመር ላይ ያሉ የጤናና የማህበራዊ ዋስትና መርሃ ግብሮች አሉን ። አንድ ቦታ ላይ ወይ የእነዚህን መርሃ ግብሮች ስፋት መቀነስ አለያም የግብር ገቢያችንን ማሳደግ ወይም ደግሞ ሁለቱም አቀናጅተን ማስኬድ መቻል ይኖርብናል ። »
ምንም እንኳን አሁን የተገኘው መፍትሄ ጊዜያዊ ቢሆንም ሁለቱ ወገኖች መግባባት ላይ መድረሳቸው ለዩናይትድ ስቴትስ ትልቅ እፎይታ ነው ። ሆኖም ውዝግቡ ይህን ያህል ጊዜ መጓተት አልነበረበትም የሚሉ የፖለቲካ ታዛቢዎችም አልጠፉም ። የበጀት ቀውስ ይከተላል የሚለው ለሳምንታት የቀጠለው ስጋት ሰዎች በዩናይትድ ስቴትስ ኤኮኖሚና የዓለም መገበያያ በሆነው በዶላር ዋጋ ላይ ያላቸው እምነት እንዲሸረሸር ማድረጉን CENTER FOR AMERICAN PROGRESS የተባለው የጥናት ተቋም ባልደረባ ማይክል ዌርዝ ተናግረዋል ።
« ይህን መሰሉ ሁኔታ አንዴ ብቻ ሲደርስ በይቅርታ ማለፍ ይቻል ይሆናል ። ሆኖም ወግ አጥባቂ ሪፐብሊካኖች እንደዚህ ዓይነት ሁኔታ ውስጥ ሲከቱን በ24 ወራት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑ ነው ። ይህ ቀስ በቀስ እንደ ጥሩ አርአያ እየተወሰደ ነው ።

<a href=Senate Majority Leader Harry Reid of Nev. speaks during a news conference on Capitol Hill in Washington, Tuesday, May 15, 2012, following a political strategy meeting. (Foto:J. Scott Applewhite/AP/dapd)
” src=”http://www.dw.de/image/0,,15956183_404,00.jpg” width=”340″ height=”191″ border=”0″ />
ሃሪ ሪድ

ይህ ደግሞ ዩናይትድ ስቴትስ እንደ ዓለም የፖለቲካ ና የምጣኔ ሃብት መሪነት የተጣለባትን አመኔታ ያናጋል ።»
ለ2 ሳምንት የተወሰኑ የፌደራል መንግስት መሥሪያ ቤቶች መዘጋታቸው አሜሪካንን ተዓማኒነትን ከማሳጣቱም በላይ የ24 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ተጨማሪ ወጪም እንዳስከተለባትም የምጣኔ ሃብt ባለሞያዎች ግምት ያስረዳል ። ይሁንና ዝርዝሩ በይፋ አልተገለፀም ። በዌርዝ አስተያየት ኦባማኬር በመባል የሚጠራው በተለይ አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የህብረተሰብ ክፍሎችን ይጠቅማል የተባለው የጤና ዋስትና መርሃ ግብር ለውጥ ሳይደረግበት የብድር ጣሪያው ከፍ እንዲል መወሰኑ ለወግ አጥባቂዎቹ ሪፐብሊካኖች በተለይም ለ ቲ ፓርቲ አባላት ከባድ ሽንፈት ተደርጎ ተወስዷል ።

ሂሩት መለሰ

አርያም ተክሌ

AUDIO <a href=http://www.dw.de/popups/mediaplayer/contentId
_17166411_mediaId_17166414

DW

Post Navigation