ታንኮች የህዝብን ጤንነት አይጠብቁም የወያኔን ስልጣን ዘመን እንጂ
ከጥቂት ቀናቶች በፊት 12 October 2013(እአአ) በዳግማዊ ምኒሊክ ሪፈራል ሆስፒታል ስር የሚገኘው የአገሪቱ ብቸኛ የአስክሬን ምርመራ ክፍል የምርመራ አገልግሎቱ እንዳቋረጠ ሰምኤተናል ደግሞም ከተለያዩ ድህረ ገጾች አንብበናል የገዥው ፓርቲ ልሳን እንደሆነ የሚታወቀው ፋና FM ሬዲዮ ደግሞ ጥቅምት 13፣ 2006 በቀትር የዜና እወጃው በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ከትናንት 10 ሠዓት ጀምሮ የኤሌክትሪክ አገልግሎት በመቋረጡ የሆስፒታሉ ታክሚዎች በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ አረዳን፡ ከዚህም ጋር በተያያዘ ማለት የኤሌክትሪክ ሀይሉ በመቋረጡ የቀዶ ጥገናና ጽኑ ህሙማን ታካሚዎች፣ ጠቅላላ ቀዶ ጥገና እና ድንገተኛ ቀዶ ጥገና ህክምና የሚሰጥባቸው ክፍሎች እንዲሁም ያለ ጊዜያቸው የተወለዱና ሙቀት የሚፈልጉ ህጻናት ሙቀት የሚያገኙባቸው ክፍሎች ሙሉ በሙሉ ስራ አቁመው እንደነበር እና የኤሌትሪክ ሃይል በመቋረጡ የተነሳ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ ለነዚህ ከሞት አፋፍ ለደረሱና በተፈጥሮ መተንፈስ ላልቻሉ ህሙማን የህክምና ባለሙያዎቹ ዓየር በእጃቸው እየጨመቁ እንደሰጡ ተነገረን::
በሌላ ዜና ድግሞ 17 October 2013 (እአአ) የአስትሪየም ሳተላይትና HIS የተባለ የባህር ላይ መርከብ ጥምር መረጃ ሰብሳቢ እንዳመለከተው በመስከረም ወር ከዩክሬን ኦክታያብርስክ ወደብ ወደ ኢትዮጵያ…
View original post 330 more words